Tuesday, July 5, 2016

(ኢሳት ዜና) በአቶ ጌታቸው አሰፋ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ የሚመራው መስራቤት ለመብት ተሟጋቹ ታማኝ በየነንና ለኢሳት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በቤተሰቦቻቸው አማካኝነት ማስጠንቀቂያ ላከ። ኢሳት የታማኝ በየነን እና ሲሳይ አጌናን መልስ ይዟል።


…"እናንተ በደል አንገፈገፈን ብላችሁ ለመብታችሁ እሰከመጨረሻው ታግላቹኋል።እናንተ በተራችሁ በበደል ላይ በደል ስትጭኑብን ፡ ኢትዮጵያን በዘረኝነት ስትቀጠቅጡና ስትዘርፉ፣ ዜጎችን በገዛ ሃገራቸው ባይተዋር ስታደርጉ ይህንን በዝምታ እንድንመለከት ማስፈራሪያ እና መደለያ መላካችሁ የሚያናድድ ቢሆንም፣ ይህ ድፍረት ይበልጥ ጉልበት እንደሰጠን ለርስዎም ሆነ በሕወሃት ለሚመራው መንግስት ማስታወስ እንሻለን። ማናቸውም ማሰፈራሪያና መደለያ እንዲሁም ቤተሰቦቻችንን በዕገታ መያዝ ከነጻነት ጉዞ አንዲት ስንዝር እንደማትመልሱን በተግባራዊ ርምጃዎቻችን የምትመለከቱት ይሆናል።"

No comments:

Post a Comment