Thursday, November 12, 2015

(ከ አ.ታ ኦሮማይ) "...አፄ ቴዎድሮስ የወቅቱ ልዕለ ኃያል ከነበረው የእንግሊዝ መንግስት ጋር መጣላታቸው ስህተት ነበር፤ ይህ ስህተታቸው ደግሞ ህይወታቸውን ለማጣታቸው ምክንያት ሆኗል፡

 
አፄ ምኒልክ ከአድዋ ድል በኋላ ኤርትራን ለጣልያን የሚለቅ ውል በመፈረም የኢትዮጵያ ሉአላዊ መሬትን አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡
ከአፄ ቴዎድሮስ አጥፍቶ ጠፊነት ስልትም እንታቀብ፤ ከአፄ ምኒልክ በሉአላዊነት የመደራደር ልምድ ደግሞ እንማር..." መለስ ዜናዊ፡፡

ምንጊዜም ቢሆን አርበኝነትን መንቀፍ፣ ማንኳሰስና ማንቋሸሽ፤ ጀግኖች አርበኞችን ደግሞ ማጥላላት፣ ማዋረድና አፅማቸውን መስደብ በባንዳነትና በአገር ክህደት ተበክሎ ከበከተ፣ ከነተበና ከበሰበሰ ስነ-ልቦና የሚመነጭ እኩይና መሰርይ ባህሪ ነው፡፡
አዎ ባንዳዎች ዓላማቸው አገር በመሸጥ ሶልዲ መልቀም፤ ህዝብን አዋርዶ መከበርና መሾም እንጂ ለአገር ዳር ድንበር ለህዝብ ክብር መሞት አይደለም፡፡ ጥላቻን አንጂ ፍቅርን ሊሰብኩ አይችሉም፤ ክህደትን እንጂ ዕምነትን ፈፅሞ ሊያስፋፉ አይችሉም፤ የአርበኝነትን ታሪክ የማጠልሸትና የማጥፋት እንጂ የማበልፀግና ለትውልድ የማስተላለፍ ፍላጎትም ሆነ ዓላማ ጨርሶ የላቸውም፤ የክህደት እንጂ የአርበኝነት ታሪክ ያንቃቸዋል አይዋጥላቸውም፤ ጀግንነት ያቅራቸዋል፤ የአገር ፍቅር ያቅለሸልሻቸዋል፡፡ ይህ ሁሉ ቁም ነገር በእነሱ ውስጥ ፈፅሞ ስለሌለ ያስቀናቸዋልም፤ ከዘመን ዘመን እየደመቀና እየገነነ እየመጣ ባለው የጀግኖች አርበኞች እፁብ ድንቅ የሚያሰኝ ገድልና የማያረጅ ስብዕና ዓይናቸው ደርሶ ደም ይለብሳል፤ ነገር ግን መሆንን አይሹም፤ ቢሹም የባንዳነት ተፈጥሯቸው ስለማይፈቅድላቸው ጭራሽ አርበኛ መሆን አይችሉም፡፡ ለእነሱ አርበኝነት ማለት ባንዳነት ብቻ ነው፤ በተወለዱ በ40 ቀናቸው በይሁዳዊነት ፀበል የተጠመቁ በመሆናቸው፡፡
ባንዳዎች አገራቸው ሆዳቸው በመሆኑ የሚሞቱት ለከርሳቸው ብቻና ብቻ ነው፡፡ ባንዳዎች ንዋይን ከማፍቀር አልፈው ያመልኩታል፤ ስለሆነም ገንዘብ ለማግኘት የማያቀርቡት የመሰዋዕትነት አይነት የለም፡፡ የአገርን መሬት ይቆርሳሉ፤ ህዝብን አሳልፈው ይሰጣሉ፡፡ 
ባንዳዎች የህልውናቸው መሰረት፣ እስትንፋሳቸው ስልጣን በመሆኑ ህይወታቸውን የሚሰውት ለእሱና ለእሱ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህም ለአገር ሲል ህይወቱን የሰዋን ሊያደንቁና ሊወዱ አይችሉም፡፡

ባንዳዎች የክብር መገለጫቸው የአገር ክህደት፣ የህዝብ ጥላቻና፣ የመንፈስ ርኩሰትና ውርደት ታሪክ በመሆኑ መሰዋዕትነትና ፍቅርን አክብሮ ለመቀበል የሚያስችል ምንም አይነት መሻት በውስጣቸው ፈፅሞ የለም፡፡
ባንዳዎች ዋነኛ ተግባራቸው የአርበኝነትን ታሪክ ከዝክረ መዝገብ መፋቅ ብቻ ሳይሆን የባንዳነት ጥቁር ጥላሸት መቀባትም ጭምር ነው፡፡ በተለይም ደግሞ እንደ እነ አፄ ምኒልክ አይነት የጥቁር ህዝብ ነፃነት ቀንዲሎች ቦግ ብለው በርተው በባንዳነት ዋሻ ውስጥ ተቀብሮ በድቅድቅ ጨለማ የተዋጠውን ማንነታቸውን አጋልጠው እርቃናቸውን ስለሚያስቀሩት አይመቿቸውም፡፡
አዎ መለስ ዜናዊ በተወለደ በአርባኛው ቀን በይሁዳዊነት ፀበል ተጠምቆ በህዝብ የጥላቻ ስነ-ልቦና ተኮትኩቶ አገር ተሸጦ የተለቀመ ሶልዲ እየበላ ያደገ አድጎም በህዝብ ውርደት ነግሶ ኖሮ በኢትዮጵያችን ላይ ታላቅ ክህደትን ፈፅሞ የሙጥኝ ብሎ ለስልጣኑ የሞተ እልምያለ የባንዳ ልጅ ባንዳ ነው፡፡
ባንዳ የባንዳ ልጅ ምንጊዜም ጠፊ ነው
እሱን እንደ አርበኞች አልፋና ኦሜጋ ያደረገው ማን ነው፤
ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በ30 ዲናር ሸጠው- በመዳፎቻቸው ሙሉ ክህደትን የዘገኑ
ቀፎውን በዘረኝነት ዘንግ በመሸንቆር ንቦችን የበተኑ
በክህደት ተጠምቀው በውሸት የፀኑ፤
ከርስ ከህሊና የበለጠባቸው
መንደር ከአገር ጎልቶ ሚታያቸው 
በደም የሰከሩ ግፍ ያሻገታቸው
ከምላስ በስተቀር ምንም የሌላቸው
ከድንቁርና አፈር በዘር ውሃ አቡክቶ ጋግሮ ያወጣቸው
በስብሰው የገሙ የቁም ሬሳዎች ዞምቢዎች ናቸው፤
ብቸኛው አማራጭ ብቸኛው መፍትሄ ከኢትዮጵያ- ጠራርጎ ቆፍሮ መቅበር ነው
መቃብራቸው ላይ "የገፋሽ ይገፋ" በማለት መፃፍ ነው፡፡

ዛሬ ላይ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ እያፋፋመው የሚገኘው የአርበኝነት ትግል ባንዳነትን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት የሚደረግ ነው፡፡
ከስንዴው ማሳ ላይ እንክርዳዶች በቅለው
ከስንዴው ጋራ በስህተት ታጭደው ተወቅተው
ታፍሰው ተሰፍረው ጎተራ ውስጥ ገብተው
ከዚያም ተፈጭተው ከስንዴው ጋር ልመው
ዳቦ ይሆናሉ ሊጥ ሆነው ተጋግረው
ዳቦውም አይጣፍጥ ይመራል ስንቀምሰው
ግን እንክርዳዶቹ ከዳቦው ውስጥ ሆነው
"ቅመም ነን" ይላሉ የበለጥን ከዳቦው 
የትናንትናውን ማንነታቸውን ፈፅመው ዘንግተው፡፡

አርበኝነት ባንዳነትን ያሸንፋል!

No comments:

Post a Comment