Thursday, November 12, 2015

“የድርቁ ጉዳይ እንቅልፍ ነስቶኛል!… የህዝብ መሆናችን የሚረጋገጥበት ሰዓት አሁን ነው” – (ቴዲ አፍሮ) -

teddy afro(ቴዲ አፍሮ) የድርቁ ጉዳይ እንቅልፍ ነስቶኛል! አንድ በጣም ሚገርመኝ ነገር አለ ፣ እኛ አርቲስቶች ትንሽ እውቅና ስናገኝ መንግስትን መተቸት ይቀነናል ። መንግስት
ን መተቸት ካለብን መተቸቱ ትክክል ቢሆንም ፣ መንግስትን መተቸት ብቻ ለኢ/ያ ህዝብ ጉርሻ ዳቦ የሚሆነው አይመስለኝም። ሁሌ ከመንግስት ጋር አተካራ ከመግጠም ይልቅ መጀመርያ የራሳችን ድራሻ ተወጥተን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን አንድ ነገር እንስራ ! በእውነቱ በየሚድያው ህዝቤ ወገኔ እያልን ስንነግድለት የነበረው ህዝባችን ነው ረሀብ እያንካካው ያለው። የህዝብ መሆናችን የሚረጋገጥበት ሰዓት አሁን ነው! አዎ አሁን በክፉው ቀን ህዝባችን ባጣበት እጁን ባጠረበት ያውም ብዙ የለመደ!! እንደ ከዚህ ቀደሙ በአውሮፓም በአሜሪካም ያሉትን የጥበብ ሰዎች እንዳይቀድሙን ፣ የአለም መሳቅያ እንዳንሆን ሰጋሁኝ ! “እኛ ነን አለም” ይህ መፈክር ብዙዎቻችን የምናውቀው ይመስለኛል። ሀገራችን በ1977 በድርቅ ስትጎዳ የሀገራችንን ህዝብ ለመታደግ የአለም አርቲስቶች በታዋቂው እንግሊዛዊው ዘፋኝ ቦብ ጊልዶፍ አስተባባሪነት የተዘጋጀ የኮንሰርት ስያሜ ነው። በዚህ ዘመን ያንን አይነት ድምበር ዘለል ድጋፍ የምንጠብቅበት አይደለም እንደውም ያልተከፍፈለ እዳ ያለብን ሆኖ ይሰማኛል። በተከሰተው የድርቅ አደጋ የተጎዳ ወገናችን መርዳቱ የመግስት ሰራ ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮያዊ ትብብርና ድጋፍ ይጠይቃል። የማይቻል የለም ራሳቸን በራሳቸን ከተባበርን ህዝባችን ከረሀቡ ልንታደገው እንችላለን ! ስለሆነም እኛ አርቲስቶች የተለያዩ ኮንሰርቶችን በማዘጋጀት የበኩላችን አስተዋፆ እንድናደርግ ጥሬዬን አቀርባሎህ። ቸሩ እግዚአብሔር አምላክ ቅድስቲትዋ አገራችን ኢትዮጵያ ሰላምዋን ጠብቆ ለዘላለም ያኑርልን። ፍቅር ያሸንፋል - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48194#sthash.RSYT7QKT.dpuf

No comments:

Post a Comment